tg-me.com/orthodox1/13094
Last Update:
. ለምን ቃና ዘገሊላ በቅዱስ ሚካኤል ቀን ዋለ?
°°°°°°°[#ነገረ_ያዕቆብ_ወልደ_ይስሐቅ]°°°°°°°°
ዛሬ የየካቲት ፳፫ቱን በገሊላ አውራጃ በቃና መንደር የተደረገ ተዓምር የምናስብበት የተውላጥ በዓል ነው።
[ተውላጥ ማለት ቅያሪ ልዋጭ ማለት ነው] አንድን ክብረ በዓል ከዕለቱ ውጪ በሌላ ቀን ለማሰብ ከሚያ’ዙ የቀኖና መንገዶች መኃል እኒኽ ሦስቱ በዋናነት ይጠቀሳሉ፤
① ራሱን ለማስቻል
ይኸውም በዕለቱ ሌላ ከብሮና ገንኖ የሚነገር ክብረ በዓል ካለ ራሱን ችሎ እንዲዘከር በተለየ ትኩረት ታስቦ እንዲከበር የዕለት ለውጥ ይደረግለታል፤
ለምሳሌ፦ የዮሐንስ አፈወርቅ ፍልሰቱን ከመስከረም ፲፯ ወደ ኅዳር ፲፯ ለማሳለፍ እንደ ምክንያት «…ይህም (ፍልሰቱ) በመድኃኒታችን በመስቀሉ በዓል መስከረም ዐሥራ ሰባት ቀን ነው ። ስለዚህም ራሱን ለማስቻል ወደ ኅዳር ዐሥራ ሰባት ቀን ለወጡት» ይለናል። እንደዚሁ ሁሉ ሌሎችም በጌታ ልደት ቀንና በሰሙነ ሕማማት የሚዘከሩ የቅዱሳኑ በዓላት ከተደራቢነት ይልቅ በተውላጥ ይከብራሉ።
② ምሥጢር ለማገናኘት
ክብረ በዓሉን የበለጠ ለማጉላት ምቹ ኩነቶች ካሉ አያይዞ በሌላ ቀን በመዘከር ስለጉዳዩ ትኩረት እንዲሰጥ ያደርጋል።
ለምሳሌ ፦ የመጋቢት ፳፱ኙን ብሥራት ወደ ታኅሳስ ፳፪ ማምጣት በዐቢይ ጾም በሰሙነ ሕማማት ከመዋሉ ባሻገር ተወለደ ለማለት ተጸነሰ የማለትን ምሥጢር እንድንዘክር ከልደቱ ፯ ቀን ቀድመን እንድንዘክር በተውላት ብሥራት ብለን እናስበዋለን፣ በተጨመሰሪም በበጋ ወራት ወደ በረሃ መሰደዷ የተነገረውን እመቤታችንን በበረሃ ያለች የማትጠወልግ አበባ ከሚል ምሥጢር እያገናኙ ሊቃውንት ዘመነ ጽጌን የስደቷ መታሰቢያ ያደርጋሉ። ያነሳነውን የዛሬ በዓልም የካቲት ፳፫ ቀን የተፈጸመ ሲሆን የቃና ዘገሊላ ተአምር በጥር ፲፪ ቀን የውኃን በዓል ከውኃ አገናኝቶ ቀኖና ቤተክርስቲያን የጥምቀት ማግሥት ይዘክረዋል።
③ ቀኖና ቤተክርስቲያን
አዋጅ ሆኖ በጉባኤ ቤተክርስቲያን የተደነገገ ቀን ሲኖር በተለይ ዐበይት በዓላትንና አጽዋማትን የሚመለከት ውሳኔዎች
ለምሳሌ፦ የመጋቢት ፬ቱ የአሞር ደሴት ጉባኤ የፋሲካ በዓል በሰንበት እንዲውል ለመጋቢት ፳፱ ተውላጥ እንዲኖረው መደንገጉ የዚህ አካል ነው። ይህ ድንጋጌ ከላይ ያሉትንም ሊያቅፍ የሚችል በተለይም በዓላት በቀን ቁጥር ከሚውሉበት እዕዋዳት ሌላ ዕለት እንዳይለቁ በማሰብ እንዲሁም በዐቢይ ጾምና ሰሙነ ሕማማት ዕረፍተ ሰማዕታት ልደተ ጻድቃን ሢመተ መላእክት እንዳይዘከር ታውጇል ይህን በመሰለው መንገድና ሌሎችም ብዙ ምክንያቶች ለለውጥ በዓላት ሊጠቀሱ ይችላሉ።
ጥምቀትና ቃና ዘገሊላ የኤጲፋንያ ክፍሎች ናቸው። ወመዋዕለ አስተርእዮ ውእቱ ኤጲፋንያ እንዲል 【ሃይ አበ ዘ፫፻ ፳፥፲፰】
ኤጲፋንያ የተባለውን አስተርእዮን ከሦስት የመገለጥ ታሪክ ጋር አያይዘው የሚያቀርቡ አሉና
፩】 የክርስቶስ ጥምቀት (the baptism of Jesus)
፪】 የሰብአ ሰገል ወደ ቤተልሔም ተጉዞ አምላክን ማየት (the visit of the Wise Men to Bethlehem)
፫】 የቃና ዘገሊላው ተአምር (the miracle at Cana)
💦 የቃና ዘገሊላውን ተኣምር ከጥምቀቱ ጋር የሚያገናኙ አያሌ ምሥጢራት እንዳሉት ሁሉ በዓለ ቅዱስ ሚካኤልን ከጥምቀትና ከቃና ዘገሊላው በዓል ጋር ምን ያዛምደዋል?
💦 ለተውላጡ ፲፪ ለምን ተመረጠ?
💦 ከቀናቱ ለምን አልቀደመ? ለምንስ አልዘገየ?
💦 ታቦተ ሚካኤልስ ምን አገናኝቶት በተለየ ዛሬ ክብረ በዓሉ ሆኖ ዋለ?
ቅዱስ ሚካኤልን በሚመለከት በስንክሳሩና በድርሳኑ ዛሬ የሚከብርበት ምክንያት እንዲህ ተዘግቦልናል።
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፤ አመ ዐሡሩ ወሰኑዩ ለወርኃ ጥር ፡ በዛቲ ዕለት ተዝካረ በዓሉ ለመልዐክ ክቡር ሚካኤል ሊቀ መላዕክት እስመ በዛቲ ዕለት ፈነዎ እግዚአብሔር ለቅዱስ ሚካኤል ሊቀ መላእክት ኀበ ያዕቆብ እሥራኤል እንዘይፈርሕ እሁ ዔሳውሃ ፡ ወአድኀኖ እምኔሁ ወአኅለፎ ፈለገ ዮርዳኖስ።
☞ በአብና በወልድ በመንፈስቅዱስም ስም አንድ አምላክ ብለን አምነን ጥር በባተ ፲፪ ቀን የሊቀመላዕክት ቅዱስ ሚካኤል በዓል ይከበር ዘንድ እንናገራለን በዚች ቀን እግዚአብሔር ሊቀ መላዕክት ቅዱስ ሚካኤልን ዕሥራኤል ወደተባለ ያዕቆብ ልኮት ከሚፈራው ወንድሙ ዔሳው ታድጐ የዮርዳኖስን ወንዝ አሻግሮታልና ::
ወሖረ ያዕቆብ ኀበ ላባ እኁሃ ለእሙ ፡ ወአስተዋሰቦ ክልዔ አዋልዲሁ ልያሃ ወራኄልሃ ። ወአግብኦ እንዘ ይጸይሕ ፍኖቶ በዳኅና ወበሰላም ምስለ ሰብኡ ወንዋዩ ወውሉዱ ወተቀበሉ እኁሁ ዔሳው በሰላም ወፍቅር
☞ ያዕቆብም ወደእናቱ ወን ድም ላባ ዘንድ በደረሰ ጊዜ ላባም ኹለቱ ልጆቹን ልያንና ራሔልን አጋባው ፡፡ መንገዱ ንም አቅንቶ በደኅና በፍቅር ከቤተሰቡና ከንብረቱ ጋራ መለሰው ፡፡ ወንድሙ በፍቅር አንድነት ተቀበለው፡፡
ወበእንተዝ አዘዙነ አበዊነ ቅዱሳን ሐዋርያት ሥዩማን ዲበ ማኅበረ ምእመናን ከመ ንግበር ተዝካረ በዓሉ ለመልዐክ ክቡር ሚካኤል ሊቀ መላዕክት አመ ዐሠሩ ወሰኑዩ ለለወርኁ ትን ብልናሁ ወአስተብቊዖቱ የሀሉ ምስሌነ ለዓለመ ዓለም አሜን
☞ ስለዚህ በማኅበረ ምእመናን ላይ የተሾሙ ቅዱሳን አበው በእየወሩ ዐሥራ ሐዋርያት ኹለት ቀን የሊቀ መላዕክት ቅዱስ ሚካኤልን ዝክረ በዓል እናደርግ ዘንድ አዘውናል ። ፍጹም አማላጅነቱ ለዘለዓለሙ ከእኛ ጋራ ይኹን አሜን 🙏
ስንክሳሩም ቢሆን የሚደግመው ይኽንኑ ነው።
ቅዱስ ሚካኤል ለያዕቆብ ስለዋለለት ውለታና ስለፈጸመለት ትድግና ራሱ እስራኤል የተባለ ያዕቆብ በአንደበቱ እንዲህ እያለ ምስክርነቱን ሠጥቷል።
“ከክፉ ነገር ሁሉ ያዳነኝ መልአክ፥ እርሱ እነዚህን ብላቴኖች ይባርክ” 【ዘፍ ፵፰፥፲፮】
ያዕቆብን ጌታችን የተጠመቀበትን ፈለገ ዮርዳኖስ አሻግሮ በመንገዱ የመራ ያሳደገው የመገበው የጠበቀው ከክፉ የታደገው ቅዱስ ሚካኤል ዛሬ በዚህ መንገድ ከታሰበ ከጥምቀት ጋር ምን አገናኝቶት ነው? የያዕቆብ ሕይወት በጥላነት ለአካሉ በምሳሌነትም ለአማናዊው ጥምቀት የጎላ ምሥጢራዊ ማነጻጸርያ ሆኖ በሊቃውንት ተተርጉሟል።
ዮርዳኖስን በመልአኩ ከመሻገሩ ባለፈ ከሁለት ክፍሎች ያገኘነውን በየተራ እንመልከት፦
፩ኛ】 ያዕቆብ ወደ ምሥራቅ ሀገር ሰዎች ሄዲ በውኃው ጉድጓድ አጠገብ ስለፈጸመው ሥራ 【ዘፍ ፳፱፥ ፪】 የምሥጢሩን ፍቺ ቅዱስ ቀሌምንጦስ ዘሮም በመጽሐፉ የተገለጠለትን የተነገረውን【መጽሐፈ ቀሌምንጦስ ፭ ፥፳፰–፴፩ 】 ከጥምቀት ጋር አገናኝቶ እንዲህ ተርጉሞታል
✧ ወሖረ ያዕቆብ እምውስተ ውእቱ መካን ኀበ ላባ እሁሃ ለእሙ ወርእየ በፍኖት ዓዘቅተ አባግዕ ወክዱን አፉሃ ለዓዘቅት በዓባይ እብን። ወራሄል ወለተላባ ትቀውም ህየ ምስለ እሉ አባግዕ ኀበ ዓዘቅት ወነሥአ ያዕቆብ ወከሰታ ለይእቲ እብን እምአፈ ዓዘቅት ወነሥአ ማሕየበ ወአስተዮን ለእሉ ፅሙዓን አባግዕ እለሐለዋ ምለስ ራሄል ወእምዝ ቀርበ ኀቤሃ ለራኄል ወሰዓመ። ወከስተ ያዕቆብ አፈዓዘቅት አምሳለ ጥምቀት ቅድስት እንተ ኮነት ኀብእተ እምትካት ዘለዓለም።
BY ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - 🇴🇷🇹🇭🇴🇩🇴🇽 🇹🇪🇼🇦🇭🇩🇴
Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 283
Share with your friend now:
tg-me.com/orthodox1/13094